- Legal Name: Gerese DebreMenkrat Metmeke Melkot Kidus Yohanis
- Fundraising Since: 26 mar 2026
Gerese DebreMenkrat Metmeke Melkot Kidus Yohanis
ለተአምረኛው ለገረሴ መ/መ/ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ መቅደስ እንሥራ!
የአርባምንጩ ተአምረኛው የገረሴ ዮሐንስ ምዕመናን ከአራቱም ማዕዘን የኢትዮጵያ ክፍል እየመጡ ከጨጓራ ካንሰር፣ ከአንጀት ካንሰር፣ ከደም ካንሰር፣ ከኩላሊት፣ ከእንቅርት በሽታ የሚፈወሱበት ድንቅ ቦታ ነው:: በአልጋ መጥተው ቆመው ይሄዳሉ፣ እግራቸው ያበጠ መቆም ያቃታቸው ቁመው እንዲመለሱ አድርጓቸዋል በልጅ ማጣት የሚሰቃዩ እናቶች ልጅ እየተሰጣቸው በልጆቻቸው ተደስተዋል፡፡
በመሆኑም የፀበሉ ፈዋሽነት በዓለም ስለታወቀ ወደዚህ ስፍራ ከሁሉም ቦታ ስለሚመጡ በቤተመቅደሱ ውስጥ ገብተው ህሙማን ንስሀ ገብተው ሚስጢራት መፈፀም ቀርቶ ለአምስቱ ልዑካን በሚገባ ዑደት እየፈፀሙ መቀደስም ሆነ ህዝቡም ማስቀደስ ስለተቸገሩ አሁን በመገንባት ላይ ያለው ቤተ መቅደስ ሊታነፅ ችሏል፡፡
ይህም ቤተመቅደሱ እስካሁን ድረስ ወደ 35,000,000 ብር (ሰላሳ አምስት ሚሊየን ብር) በሚጠጋ ወጪ የመሠረትና ወለል ላይ ያሉ ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን ቀሪ ሥራዎችን ሰርቶ ቤተመቅደሱን ለፍጻሜለማድረስ እስከ 108,000,000 ብር (አንድ መቶ ስምንትሚሊየን) ድረስ የሚገመት ወጪ የሚያስፈልገው ስለሆነና የገረሴ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተመቅደሱ እንዲታነፅ በአካባቢው ያሉ ምዕመናን በቂ ስላልሆኑ በዓለም ለሚገኙ ለዮሐንስ ወዳጆች ለመንገር ስለተገደድን መጋቢት 18፣ 19 እና 20 የቀጥታ ስርጭት ስለምናደርግ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ወዳጆች የተዋሕዶ ልጆች የቅዱስ ዮሐንስ ውለታ ያለባችሁ ሁሉ ይህንን ቤተ መቅደስ ተረባርበን እንድንሰራው መጋቢት 18፣ 19እና 20 በመላው ዓለም የሚተላለፍ የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ ተዘጋጅቷልና ድጋፍ እንድታደርጉልን ስንል በመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ስም እንማፀናችኋለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ :-
ንገድ 1000715788927
አሐዱ 0087756711701
አዋሽ 013521729471101
አባይ 9521112935265010
አቢሲንያ 249578207
ስልክ:-
0911636818
0925555566
0931223355
0938464646
Whatever you choose, thank you!
Copyright 2026 - Wegenfund | Powered by WegenTech