- Started on: 27 feb 2024
- Closing Date: 30 jun 2024
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
“ድረሱልን፣ አጥምቁን እና ወደ ቀደመችው ሃይማኖታችን መልሱን”
የቅድስት ቤተ ክርስቲያናን ተቀዳሚ ተልዕኮ ቅዱስ ወንጌልን ለዓለም ሁሉ በማ ዳረስ የሰው ልጅን ለእግዚአብሔር መንግሥት ማብቃት ነው። በሀገራችን ጠረፋማው ክፍል የሚኖሩ ወገኖችን በማስተማር፣ ማጥመቅ እና ማጽ ናት ረገድ የተሠራው ሥራ በእጅጉ ውስን ነው።
“ድረሱልን፣ አጥምቁን እና ወደ ቀደመችው ሃይማኖታችን መልሱን” እያሉ የሚጣሩ ነፍሳት ቁጥር እጅግ ብዙ ነው። የቅድመ ጥምቀት የሃይማኖት ትምህርት ለማስተማር፣ ለማጥመቅ፣ በአፍ መፍቻ ቋንቋ የሚያስተምሩ መምህራንን ለማሰልጠን፣ መጽሐፍትን ለመተርጎም እና መም ህራንን ለመቅጠር በአጠቃላይ ክርስትናን በጠረፋማ አካባቢዎች ተደራሽ ለረድሽ ግ የሁላችንንም ተሳትፎ እና ድጋፍ ይጠይቃል።
ስለሆነም ይህን መንፈሳዊ ተልእኮ እንዲደግፉ በልዑል እግዚአብሔር ስም መን ፈሳዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ማኀበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል
Copyright 2024 - Wegenfund | Powered by WegenTech