አስቸኳይ የዕርዳታ ጥሪ ለዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት ካህናትና አብያተ ክርስቲያናት

cause-image
  • Started by: Hailu Reda
  • For: photo_2022-01-25_21-40-12.jpg
  • Started on: 27 jan 2022
  • Closing Date: 31 mar 2023

በሀገራችን ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት እና ጦርነቱ ባስከተላቸው ቀውሶች ምክንያት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን፣ ኦርቶዶክሳውያንና ሌሎች ዜጎች ለከፋ ችግር እየተጋለጡ ይገኛሉ። ጦርነቱ ከባድ ጉዳት ካደረሰባቸው አካባቢዎች መሃል የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት አንዱ ነው (ሰቆጣ እና አካባቢው)። በዚህ አካባቢ ከአምስት ወር በላይ በተካሄደው ጦርነት ብዙ ዜጎች ሕይወታቸው አልፏል፣ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል፣ አብያተ ክርስቲያናት ወድመዋል፣ ጉባኤ ቤቶች ተፈትተዋል፣ ገዳማውያንና ዜጎች ፈልሰዋል።

በአሁኑ ወቅት አንጻራዊ ሰላም ቢኖርም የአካባቢው አባወራዎች ከነቤተሰቦቻቸው ከዕለት ጉርስ ጀምሮ ልዩ ልዩ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል፣ ከ600 በላይ የሚደርሱ አብያተ ክርስቲያናት መቀደሻ ዕጣን እና ጧፍ የላቸውም፣ አገልጋይ ካህናት እንዲሁም የአብነት መምህራን እና ተማሪዎችም ምግብ እና መሠረታዊ ፍላጎቶች የሚያስፈልግበት ወቅት ነው። ስለሆነም በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ለወገናችሁ በምትችሉት ሁሉ በዚህ በወገን ፈንድ በኩል ርዳታችሁን እንድታደርሱልን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን
የዋግ ኽምራ ሀገረ ስብከት

Collections so far

(Rounded figure - does NOT affect actual money deposited)

ETB 763,082 of ETB 1,200,000 64%